ስለ አገልግሎታችን
የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና አገልግሎት ለማን ያስፈልጋል? ምንስ ይጠብቅዎታል?
የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና (MNCH) አገልግሎቶች ታስበው የተዘጋጁት በእርግዝና፣ በወሊድ እና በቅድመ-ልጅነት ጊዜ ውስጥ ቀጣይነት ያለው እና ጥራት ያለው እንክብካቤ ለሚያስፈልጋቸው ሴቶች፣ ጨቅላዎች፣ ሕፃናት፣ ታዳጊዎች እና ቤተሰቦች—በተለይም በቂ አገልግሎት ላላገኙ እና ተጋላጭ ለሆኑ ማህበረሰቦች—ነው። በኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE)፣ እነዚህ አገልግሎቶች የእናቶችን እና የሕፃናትን ጤና እና በሕይወት የመኖር ዕድል የሚደግፉ ሲሆን፣ ሊቀሩ የሚችሉ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ሞትን ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ማኅበሩ (FGAE) የተቀናጁ እና ጥራታቸውን የጠበቁ ተቋማዊና ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶችን በመጠቀም፤ የቅድመ ወሊድ ክትትልን (ANC)፣ በባለሙያ የታገዘ የወሊድ አገልግሎትን፣ ከወሊድ በኋላ የሚደረግ ክትትልን (PNC)፣ የሕፃናት ጤና አገልግሎቶችን፣ የክትባት አገልግሎትን (EPI)፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍ የኤች.አይ.ቪ መከላከልን (PMTCT)፣ የተዋልዶ ጤና ምክርን፣ የአባላዘር በሽታዎችና የኤች.አይ.ቪ ምርመራና ምክርን፣ አጠቃላይ የጽንስ ማቋረጥ እንክብካቤን (CAC)፣ እንዲሁም የሪፈራልና የትስስር አገልግሎቶችን ያካተተ ሁለንተናዊ የእናቶችና ሕፃናት ጤና እንክብካቤ ይሰጣል። ተገልጋዮች በሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጡ አክብሮት የተሞላባቸው እና ተገልጋይን ማእከል ያደረጉ አገልግሎቶችን፤ የቤተሰብ ጤና ኔትወርክ (FHN) ክሊኒኮችን ጨምሮ በተለያዩ የአገልግሎት መስጫ አማራጮች ማግኘት ይችላሉ። ይህም ለሴቶችና ለሕፃናት የአገልግሎት ተደራሽነትን፣ ጥራትን እና ያልተቋረጠ እንክብካቤን ያጠናክራል።

የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና አገልግሎት ከእንክብካቤ በላይ ነው — የሕይወት መታደጊያ ጭምር እንጂ!
የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና (MNCH) አገልግሎቶች የሴቶችን፣ የጨቅላዎችን፣ የሕፃናትን እና የታዳጊዎችን በሕይወት የመኖር ዕድል፣ ጤና እና ደህንነት ይደግፋሉ—በተለይም በቂ አገልግሎት ባላገኙ እና ተጋላጭ በሆኑ ማህበረሰቦች ውስጥ። ማኅበሩ (FGAE) በሚያከናውናቸው አጠቃላይ የተዋልዶ ጤና ፕሮግራሞች አማካኝነት፣ ሊቀሩ የሚችሉ የእናቶችና የሕፃናት ሞትን ለመከላከል አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሲሆን፤ ከአገራዊና አህጉራዊ የጤና ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ጋር በተጣጣመ መልኩ ጤናማ እርግዝና፣ አስተማማኝ ወሊድ እና የሕፃናት እድገት እንዲረጋገጥ ይሰራል::
ሁለንተናዊ እና የተቀናጀ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና እንክብካቤ
የኢትዮጵያ የቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE) ሰፊ የሆኑ የእናቶችና ሕፃናት ጤና አገልግሎቶችን ይሰጣል። እነዚህም የቅድመ ወሊድ ክትትልን (ANC)፣ በባለሙያ የታገዘ እና በተቋም ውስጥ የሚሰጥ የወሊድ አገልግሎትን፣ ከወሊድ በኋላ የሚደረግ ክትትልን (PNC)፣ የሕፃናት ጤና አገልግሎቶችን፣ የክትባት አገልግሎትን (EPI)፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍ የኤች.አይ.ቪ መከላከልን (PMTCT)፣ የአባላዘር በሽታዎችና የኤች.አይ.ቪ ምርመራና ምክርን፣ አጠቃላይ የጽንስ ማቋረጥ እንክብካቤን (CAC)፣ እንዲሁም የሪፈራልና የትስስር አገልግሎቶችን ያካትታሉ። አገልግሎቶቹ በእናቶችና ሕፃናት የጤና ጉዞ ውስጥ ያልተቋረጠ እንክብካቤ መኖሩን ለማረጋገጥ፤ የቤተሰብ ጤና ኔትወርክ (FHN) ክሊኒኮችን ጨምሮ በተለያዩ የአገልግሎት መስጫ አማራጮች አማካኝነት ይቀርባሉ።
ርህራሄ የተሞላበት፣ በሙያ የበለፀገ እና ተገልጋይን ማእከል ያደረገ አገልግሎት
ሁሉም የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና (MNCH) አገልግሎቶች በሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎች እና በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነት፤ አክብሮት የተሞላበት እና ተገልጋይን ማእከል ያደረገ አቀራረብን በመከተል ይሰጣሉ። ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስራዎች፣ የጤና ተቋማትን ማዘመን እና የአገልግሎት ጥራት ቁጥጥር መደረጉ፤ ሴቶች፣ ጨቅላዎች እና ሕፃናት በእያንዳንዱ የሕይወት ምዕራፍ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ውጤታማ እና ክብራቸውን የጠበቀ እንክብካቤ እንዲያገኙ ያረጋግጣሉ።


በጠንካራ አጋርነት የሚቀርቡ ተደራሽ አገልግሎቶች
ማኅበሩ (FGAE) የተቀናጁ ተቋማዊ አገልግሎቶችን፣ የማህበረሰብ አቀፍ ተደራሽነት ስራዎችን እንዲሁም ከመንግስት እና ከግል የጤና አጋሮች ጋር ያለውን ትብብር በመጠቀም፤ የእናቶችና ሕፃናት ጤና (MNCH) አገልግሎቶችን በተለያዩ አካባቢዎች ተደራሽ ያደርጋል። የሪፈራል ስርዓቶችን በማጠናከር፣ የአገልግሎት ጥራትን በማሻሻል እና በቂ አገልግሎት ላላገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች—ወጣቶችን ጨምሮ—ቅድሚያ በመስጠት፤ ማህበሩ አስፈላጊ የሆኑ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና እንክብካቤዎች በፍትሃዊነት መቅረባቸውን ያረጋግጣል።
የወሊድ መከላከያ አገልግሎት በቤተሰብ መምሪያ — ምክንያቱም ምርጫዎ ዋጋ አለውና!
በኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE)፣ የእርግዝና መከላከያ አገልግሎቶች ግለሰቦች እና ጥንዶች ስለ ልጆቻቸው ብዛት፣ አራርቆ መውለድና እና የመውለጃ ጊዜ ላይ በእውቀት ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንዲያስተላልፉ ያስችላሉ። ማኅበሩ ትክክለኛ መረጃን፣ የምክር አገልግሎትን እና ሁሉንም ዓይነት የቤተሰብ እቅድ ዘዴዎችን በማቅረብ፤ የጋብቻ ሁኔታ ሳይገድበው ለአገልግሎቱ ብቁ ለሆኑ ተገልጋዮች በሙሉ በእውቀት ላይ የተመሠረተ ምርጫን፣ ጥራት ያለው እንክብካቤን እና የተሻሻለ የተዋልዶ ጤናን ያበረታታል።
የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና አገልግሎቶች ጥቅሞች
የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና አገልግሎቶች ትኩረት የሚያደርጉት በሴቶች፣ በጨቅላዎች፣ በሕፃናት እና በታዳጊዎች ደህንነት እና በሕይወት የመኖር ዕድል ላይ ነው። የተቀናጁ የእናቶችና ሕፃናት ጤና አገልግሎቶችን ተደራሽነት በማጠናከር፣ እነዚህ ፕሮግራሞች ሊከላከሏቸው የሚችሉ የእናቶችና ሕፃናት ሞትን ለመቀነስ እንዲሁም አገራዊና አህጉራዊ የጤና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ግቦች ለማሳካት አስተዋጽኦ ያበረክታሉ። በሁለንተናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ አማካኝነት፣ የእናቶችና ሕፃናት ጤና (MNCH) አገልግሎቶች በእርግዝና፣ በወሊድ እና በቅድመ-ልጅነት ወቅት ያሉ የጤና ፍላጎቶችን በተለይም በቂ አገልግሎት ላላገኙና ተጋላጭ ለሆኑ ማህበረሰቦች ምላሽ ይሰጣሉ።
ወደ ክሊኒካችን ሲመጡ ምን ይጠብቃችኋል?
በኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE)፣ የሴቶችን፣ የጨቅላዎችን፣ የሕፃናትን እና የታዳጊዎችን ጤና እና ደህንነት ለመጠበቅ፤ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና አገልግሎቶች በተቀናጁ የአገልግሎት አሰጣጥ ዘዴዎች ይሰጣሉ። ወደ ክሊኒኮቻችን በሚመጡበት ወቅት፣ አገልግሎቶቹ በሰለጠኑ ባለሙያዎች አማካኝነት ከእርግዝና እስከ ወሊድ እና ከወሊድ በኋላ ያለውን ሙሉ የእንክብካቤ ሂደት (Continuum of Care) ባካተተ መልኩ ይቀርባሉ።
01
መረጃ፣ ግንዛቤ እና ምክር
ማኅበሩ በእናቶች፣ በጨቅላ ሕፃናት እና በልጆች ጤና (MNCH)፣ በተዋልዶ ጤና (SRH)፣ በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍ የኤች.አይ.ቪ መከላከል (PMTCT) እንዲሁም ጥንቃቄ በጎደለው መንገድ የሚፈጸም የጽንስ ማቋረጥን በመከላከል ዙሪያ ሰፊ የጤና ትምህርት እና የምክር አገልግሎት ይሰጣል፡፡
02
ክሊኒካዊ አገልግሎቶች እና ሙያዊ እንክብካቤ
የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE) የቅድመ ወሊድ ክትትል (ANC)፣ በባለሙያ የታገዘ የወሊድ አገልግሎት፣ ከወሊድ በኋላ የሚደረግ ክትትል (PNC)፣ የሕፃናት ጤና ጥበቃ፣ ክትባት፣ አጠቃላይ የጽንስ ማቋረጥ እንክብካቤ (CAC)፣ የካንሰር ቅድመ ምርመራ፣ የመካንነት (የመውለድ ችግር) ሕክምና እና በጾታ ላይ ለተመሠረተ ጥቃት (GBV) የሚሰጡ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎቶችን በጥራትና በምስጢር ያቀርባል።
03
የተቀናጀ እንክብካቤ፣ ሪፈራል እና ክትትል
በተቀናጁ ክሊኒኮች በኩል አገልግሎቶች በሪፈራል፣ ክትትል እና ቀጣይነት ባለው ድጋፍ ይሰጣሉ።

ለእናቶች፣ ለጨቅላ ሕፃናት እና ለልጆች ጤና አብረውን ይቁሙ!
- የተቀናጁ የእናቶችና ሕፃናት ጤና (MNCH) አገልግሎቶች ተደራሽነት፦
ማኅበራችን (FGAE) የሴቶችን፣ የጨቅላዎችን፣ የሕፃናትን እና የታዳጊዎችን ጤና እና ደህንነት ለመጠበቅ፤ የተቀናጁ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤና አገልግሎቶችን በቤተሰብ ጤና ኔትወርክ (Family Health Network) ክሊኒኮች እና በተለያዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ዘዴዎች ተደራሽ ያደርጋል። ይህም በተለይ በቂ አገልግሎት ያላገኙ እና ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰቦችን ታሳቢ ያደረገ ነው። - ጥራት ያለው እንክብካቤ በሁሉም ደረጃዎች፦
በሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎች የተቀናጁ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቶችን በመጠቀም፤ የቅድመ ወሊድ ክትትልን፣ በባለሙያ የታገዘ የወሊድ አገልግሎትን፣ ከወሊድ በኋላ የሚደረግ ክትትልን፣ የሕፃናት ጤናን፣ ክትባትን፣ የተዋልዶ ጤና አገልግሎቶችን እና የሪፈራል ትስስርን ያካተቱ የተሟሉ የእናቶችና ሕፃናት ጤና (MNCH) አገልግሎቶች ይሰጣሉ።
የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የልጆች ጤናን ማሻሻል ሊከላከሏቸው የሚችሉ የሞት አደጋዎችን ለማስቀረት፣ እንዲሁም አገራዊ እና አህጉራዊ የልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ ነው። የኢትዮጵያ የቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE) ጥራት ያላቸውና የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ፣ የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት፣ የጤና ተቋማትን በማዘመን፣ እንዲሁም በቅንጅት እና ቀጣይነት ባለው የአገልግሎት ማሻሻያ በቂ አገልግሎት ያላገኙ ማህበረሰቦችን ተደራሽ በማድረግ የእናቶችና ሕፃናትን ጤና ፍላጎቶች ለማሟላት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
















